በ16 ተሽከርካሪ ወደ መሀል ሀገር ሊገቡ የተዘጋጁ 525 ሚሊየን 245 ሺህ ብር ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ ዕቃዎች በትናንትናው ዕለት በሶማሌ ክልል ቢዮባሃይ በተባለ አካባቢ ተያዙ፡፡
የኮንትሮባንድ ዕቃዎቹ ሊያዙ የቻሉት የሶማሌ ክልል መንግሥት የፀጥታ አካላት፣ የሀገር መከላከያ እና የፌደራል ፖሊስ ከጉምሩክ ኮሚሽን ጋር ባደረጉት የተቀናጀ ክትትል መሆኑ ተገልጿል፡፡
ከተያዙት የኮንትሮባንድ ዕቃዎች መካከልም አልባሳት፣ የተሽከርካሪ መለዋወጫዎች፣ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች፣ መድኃኒት፣ ሲጋራ፣ የቤት ክዳን ቆርቆሮ እና ሌሎችም ይገኙበታል ተብሏል፡፡
በድርጊቱ የተሳተፉ አካላትን በቁጥጥር ሥር ለማዋል የክትትል ሥራዎች ተጠናክረው መቀጣላቸውን የጉምሩክ ኮሚሽን መረጃ አመላክቷል፡፡
EBC
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች