በአዘርባጃን በይፋዊ የሥራ ጉብኝት ላይ የሚገኙት የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ከአገሪቱ የኢኮኖሚ ሚኒስትር ሚካይል ጃባሮቭ ጋር ፍሬያማ ውይይት አድርገዋል።በውይይቱም የሁለቱን አገራት የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት በሚያረጋግጡ ጉዳዮች ዙሪያ በትብብር ለመስራት ከስምምነት ላይ ተደርሷል።በኢትዮጵያ ያለውን አስተማማኝ የመልማት ጸጋ እና ዕድል ለመጠቀም፣ በተለይም ገቢን ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት አዘርባጃን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኗን ሚካይል ጃባሮቭ ገልጸዋል። በኢንቬስትመንትና በስትራቴጂያዊ ስራዎች ያላትን ልምድ ለማካፈልም አገሪቱ ፍላጎት እንዳላት ሚኒስትሩ ተናግረዋል።በተጨማሪም አገሪቱ በጋራ መልማት የሚያስችሉ ዕድሎችን ሁሉ ለመጠቀም ያላትን ቁርጠኝነት ማረጋገጣቸውን ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
EBC
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች