
ኳታር ባለሃብቶች በኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች መዋዕለ ንዋያቸውን ማፍሰስ እንደሚፈልጉ ተገለጸ፡፡በኳታር፣ የመን እና ኢራን የኢፌዲሪ አምባሳደር ፈይሰል አልይ ከኳታር የኢንቨስትመንት ባለስልጣን የአፍሪካ ዳይሬክተር ሱልታንአል ሳዓዲ እና ልዑካቸው ጋር ተወያይተዋል፡፡አምባሳደር ፈይሰል÷ በኢትዮጵያ በሆቴል ቱሪዝም፣ በታዳሽ ኃይልና በአምራች ኢንዱስትሪ የኢንቨስትመንት ዘርፍ የውጭ ኩባንያዎች እንዲሰማሩ ምቹ ሁኔታዎች መፍጠራቸውን አስረድተዋል፡፡የኳታር ኢንቨስትመንት ባለስልጣን የሀገሪቱ ባለሃብቶች በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት አማራጮች መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ የበኩሉን ጥረት እንዲያደርግም ጠይቀዋል፡፡ ሱልታንአል ሳዓዲ በበኩላቸው÷ የኳታር ባለሃብቶች በኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች ኢንቨስት የማድረግ ፍላጎት እንዳላቸው መናገራቸውን የኤምባሲው መረጃ ያመላክታል፡፡
FBC
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች