

በርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ የተመራው የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ወደ ኦሞ ኩራዝ ቁጥር 3 ስኳር ፋብሪካ የስራ እንቅስቃሴን ለመመልከት በስፍራው ተገኝተዋል ።
በጉብኝቱ ርዕሰ መስተዳድሩን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣የምዕራብ ኦሞና ካፋ ዞን አመራሮች የተገኙ ሲሆን የኢትዮጵያ ስኳር እንዱስትሪ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ወዮ ሮባ እና የፋብሪካዉ አመራሮች አቀባበል አድርጎላቸዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩና ልዑካቸዉ ሁለት ቀን በሚኖራቸዉ ቆይታ የፋብሪካዉን የስራ ዕንቅስቃሴ፣የእርሻ ሁኔታ እና የምርት ሂደት እንዲሁም በምዕራብ ኦሞ ዞን እየተሰሩ ያሉ የመንገድና የኢንቨስትመት ፕሮጀክቶች በመጎብኘት በነገው ዕለት ከሚመለከታቸዉ አካላት ጋር ውይይት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል ሲል የዘገበው የክልሉ የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ነው።
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች