በፎክስ ኒውስ አዘጋጅነት በሚካሄደው የምርጫ ክርክር ላይ ተመልካቾች እንዲታደሙ ተፈቅዷል
ሁለተኛው ዙር ክርክር የምርጫውን አሸናፊነት ይወስናሉ ከሚባሉ ግዛቶች መካከል አንዷ በሆነችው ፔንሴልቬንያ ይካሄዳል
የሪፐብሊካኑ እጩ ዶናልድ ትራምፕ ባይደንን ተክተው የዴሞክራት እጩ እንደሚሆኑ ከሚጠበቁት ካማላ ሃሪስ ጋር በሁለተኛው ምርጫ ክርክር ለመሳተፍ ተስማምተዋል፡፡
በአሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ የተካሄደው የመጀመርያ ዙር ክርክር የባይደንን የዴሞክራት እጩነት አስከፍሏል፡፡
በሲኤንኤን አዘጋጅነት ያልተመልካች በዝግ ስቱድዮ በተደረገው ክርክር ሀሳባቸውን በቅጡ መግለጽ ሲሳናቸው የታዩት ጆ ባይደን ከእጩነት እንዲነሱ ተቃውሞ በርትቶባቸው ከምርጫው እራሳቸውን ማግለላቸው የሚታወስ ነው፡፡
ለ90 ደቂቃ በተካሄደው ክርክር ዶናልድ ትራምፕ አንዳንድ ከእውነታነት ከራቁ ሃሳቦቻቸው ጭምር በባይደን ላይ ብልጫ እንደወሰዱ ብዙዎች ተስማምተዋል፡፡
More Stories
እየተጠናከረ የመጣው የብሪክስ ሀገራት ግንኙነት…
አሜሪካ ሶሪያን አጠቃች
የሩሲያ ጦር በፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን መኖሪያ ቤት ላይ ተፈጽሟል ላለው ጥቃት አፀፋ በዩክሬን ላይ መጠነ ሰፊ ጥቃት መፈጸሙን አስታውቋል።