የቀዳማዊት እመቤት ጽሕፈት ቤት ከጉድ ኔበርስ ዓለም አቀፍ በጎ አድራጎት ድርጅት ጋር በጋራ ለመሥራት የሚያስችል የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል።
ዋናው መቀመጫው እና የተመሠረተበት ሀገር ደቡብ ኮሪያ ከሆነው ጉድ ኔበርስ ዓለም አቀፍ በጎ አድራጎት ድርጅት ጋር በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት መደረሱን የቀዳማዊት እመቤት ጽሕፈት በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ባሰፈርው መልዕክት አስታውቋል።
ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በመልዕክቱ እንደገለጹትም፤ ከበጎ አድራጎት ድርጅቱ ጋር በፅሕፈት ቤታቸው እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎችን ለመደገፍ እና በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን ውይይት አድርገዋል።
በውይይቱም ወደ ስራ የሚያስገባ የመግባቢያ ሰነድ መፈራረማቸውን ነው ቀዳማዊት እመቤቷ የጠቀሱት፡፡
EBC
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።