ማሻ፤ የካቲት 30/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) ዓለም አቀፉ የነዳጅ ዋጋ ከፍተኛ ጭማሪ ማሳየቱ ተሰምቷል።
በመካከለኛው ምስራቅ በተፈጠረው ቀውስ ሳቢያ አሁን ላይ አንድ በርሜል ድፍድፍ ነዳጅ ከ110 ዶላር በላይ በሆነ ዋጋ እየተሸጠ ይገኛል።
ይህም ከፈረንጆቹ 2022 ጀምሮ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው ተብሏል።
የንግድ መርከቦች መተላለፊያ የሆነው የሆርሙዝ ወሽመጥም የተዘጋ ሲሆን፥ አሜሪካ እና እስራዔልም የኢራንን የነዳጅ ማከማቻዎች በሚሳኤል ማውደማቸው ታውቋል።
ይህን ተከትሎ የነዳጅ ዋጋ ከፍተኛ ጭማሪ ያሳየ ሲሆን፥ በእስያም ከ114 ዶላር በሆነ ዋጋ እየተሸጠ መሆኑን ቢቢሲ በቢዝነስ ዘገባው አመላክቷል።
ከዚህ ባለፈም በተለያዩ አካባቢዎች የአክሲዮን ገበያ ከፍተኛ ቅናሽ ማሳየቱንም ዘገባው አመላክቷል።
ከዚህ ጋር በተያያዘም ቻይና የተፈጠረው ቀውስ የሚፈታበትን መንገድ ለማመቻቸት ልዑኳን ወደ ሳዑዲ የላከች ሲሆን፥ የቡድን ሰባት አባል አገራት ሚኒስትሮች ደግሞ በነዳጅ ዋጋ ላይ ለመምከር ዛሬ ይሰበሰባሉ።
#(አራዳ ኤፍ ኤም)
More Stories
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ኅብረት የሰው ሠራሽ አስተውሎት እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ ሆነው በአፍሪካ ኅብረት ጉባኤ ተሾሙ
ቻይና ለመጀመሪያ ጊዜ የጠፈር ጣቢያዋን ለውጭ ሀገር ጠፈርተኞች ክፍት አደረገች
ኢትዮጵያ ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር የሚላመድና የማይበገር የልማት ግስጋሴዋን በተጨባጭ ውጤቶች እያስመሰከረች ቀጥላለች።