ማሻ፤ የካቲት 3/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) ከየካቲት 4 እስከ 5 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚከበረዉ የማጃንግ ብሔረሰብ ቋንቋና ባህል ሲምፖዚየም የቅድመ ዝግጅት ስራዎች መጠናቀቃቸውተገልጿል ።
የበዓሉን ቅደመ ዝግጅት ስራዎች በማስመልከት መግለጫ የሰጡት የማጃንግ ቋንቋና ባህል ሲምፖዚየም ሰብሳቢ አቶ ዮሐንስ በንዲ እንደገለጹት ከየካቲት 4 እስከ 5 ቀን 2018 ዓ.ም በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ ለሚከበረዉ የማጃንግ ብሔረሰብ ቋንቋና ባህል ሲምፖዚየም የቅድመ ዝግጅት ስራዎች መጠናቀቃቸውን ገለጸዋል ።
የበዓሉ መከበር የብሔረሰብን ባህል፣ታሪክ፣እና ቋንቋን ከማሳደግ ባለፈ ለልማት እና ለሰላም ዕሰት ግንባታ የሚያበረክተው አስተዋጽኦ የጎላ መሆኑን የገለፁት አቶ ዮሐንስ ይህንኑ ይበልጥ ለማጠናከር ይሰራል ብለዋል ።
ለረጅም ዓመታት ተዘንግተው የቆዩ የማጃንግ ብሔረሰብ ባህላዊ እሴቶችንና የአኗኗር ዘይቤዎችን እንደገና ለማነቃቃት ያለመ ሲምፖዚየም መሆኑንም ጭምር አቶ ዮሐንስ ጠቁመዋል ።
ከየካቲት 4 እስከ 5 ቀን 2018 ዓ.ም በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ በሚከበረዉ የማጃንግ ብሔረሰብ ቋንቋና ባህል ሲምፖዚየም ላይ የባህል ትርኢቶች ፣ የምግብ አውደ ርዕይን ጨምሮ የማጃንግ ቋንቋና ባህልን የሚዳስሱ ጥናታዊ ጽሑፎች ቀርበው ውይይቶች እንደሚደረጉ ጠቁመዋል ።
በሲምፖዚየሙ ላይ ከጋምቤላ፣ ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የብሔረሰቡ ተወላጆችና ተጋባዥ እንግዶች ፣ የዩኒቨርሲቲ ምሁራንን ጨምሮ ፣የሌሎች ብሔረሰቦች ተወካዮች እንደሚሳተፉ ተገልጿል
More Stories
ለ7ኛዉ ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ የብልፅግና ፓርቲ ይምረጡኝ ቅስቀሳና የድጋፍ ሰልፍ በአንድራቻ ወረዳ ጌጫ ከተማ ተካሂደዋል ።
ጋዜጠኞች ሙያቸውን እና ሕግን እንዴት መከተል እንዳለባቸው ሊያውቁ ይገባል – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።