ማሻ፤ የካቲት 3/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8)የክልሉ ርዕሰ መስተዳድሩን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የክልልና የኮንታ ዞን አመራሮች የአመያ ከተማ የኮሪደር ልማት ፣የጪዳ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ እንዲሁም ሌሎች የልማት ስራዎች ጎብኝተዋል።
ክልሉ ተከማችተው የነበሩ ዕዳዎችን በማቅላል ወደ ምንዳነት በማሸጋገር በርካታ የልማት ስራዎችን በማስመረቅና አዳዲስ ፕሮጀክቶችን በመቅረጽ የመሰረት ድንጋይ በመስቀመጥ የህዝቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ ይገኛል።
ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)የጪዳ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅን ምልከታ ባደረጉበት ወቅት እንደገለጹት ፍጥነትና ጥራትን ማዕከል በማድረግ ግንባታው በተያዘለት የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅ አስገንዝበዋል።
በግንባታው ሂደት የታዩ ችግሮችን ነቅሶ በመለየት ለችግሮቹ መፍትሔ አካል በመሆን ግንባታው አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት በትጋት መስራት ይጠበቃል ብለዋል። ዘገባው የክልሉ መ/ኮ ነው
More Stories
ለ7ኛዉ ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ የብልፅግና ፓርቲ ይምረጡኝ ቅስቀሳና የድጋፍ ሰልፍ በአንድራቻ ወረዳ ጌጫ ከተማ ተካሂደዋል ።
ጋዜጠኞች ሙያቸውን እና ሕግን እንዴት መከተል እንዳለባቸው ሊያውቁ ይገባል – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።