ማሻ፣ ታህሳስ 25/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍኤም 103.8) በሞሮኮ እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሴኔጋል ሱዳንን 3 ለ 1 በማሸነፍ ሩብ ፍጻሜውን ተቀላቅላለች።
ምሽት 1 ሰዓት ላይ በተካሄደው የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ሴኔጋል ፓፔ ጉዬ (ሁለት) እና ምባዬ ባስቆጠሯቸው ሶስት ግቦች ሱዳንን አሸንፋለች።
ሱዳን ከሽንፈት ያልታደጋትን ብቸኛ ግብ አሚር አብደላህ ከመረብ አሳርፏል።
ጨዋታው ምሽት 4 ሰዓት ላይ ቀጥሎ ሲካሄድ ማሊ እና ቱኒዚያ የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል።
More Stories
የ2026 የካራባኦ ዋንጫ ፍፃሜ …
ሴኔጋል የአፍሪካ ዋንጫ ሻምፒዮንነቷ እንዲሰረዝ መወሰኑ አሳፋሪ ነው፡- የካፍ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ኦጉስቲን ሴንግሆር
ቦርንማውዝ ከ ማንችስተር ዩናይትድ