ማሻ ፣ የሰኔ 14፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) ፌቨን ጉርጁ ትባላለች በባህር ዳር ዩኒቨርስቲ በ2017 ዓ.ም ከአጠቃላይ የዩኒቨርሲቲው ተመራቂዎች ውስጥ 4 ነጥብ በማምጣት በባሕርዳር ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት በሳይበር ደህንነት የጥናት መስክ በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቃለች።
ፌቨን ጉርጁ ከ53 ኮርሶች 42ቱን A+ በማምጣትም የዋንጫ ተሸላሚ መሆን ችላለች፡፡
ፌቨን ዩኒቨርሰቲ ከመግባቷ በፊት በነበሩ የትምህርት ደረጃዎች ጥሩ ውጤት እያመጣች እዚህ እንደደረሰች ለኢቢሲ ተናግራለች።
ዩኒቨርስቲ ከገባሁ በኋላም ጥሩ ውጤት አምጥቼ መመረቅ ህልሜ ነበር፤ አሳክቸዋለሁም ትላለች።
ለውጤታማነቴ ከፈጣሪ በታች የቤተሰቦቼ፣ የመምህራኖች ጠንካራ ድጋፍ እና ያደረጉት ጥረት ለውጤት አብቅቶኛል ብላለች።
ኢትዮጵያ የሳይበር ደህንነት እውቀት ያላቸው የሰው ሀይል ያስፈልጋታል፤ በዚህም በተመረኩበት መስክ አገለግላለሁ ስትል የወደፊት እቅዷንም ተናግራለች።
ኢቢሲ
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።