ማሻ ፣ የሰኔ 06፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) በትራፊክ መጨናነቅ ምክንያት በረራ ያመለጣት ህንዳዊት ለበርካቶች ህይወት መጥፋት ምክንያት ከሆነው አደጋ 10 ደቂቃዎችን በመዘግየቷ መትረፏን ኤንዲ ቲቪ ዘግቧል።
ከባለቤቷ ጋር በለንደን ከተማ የምትኖረውና ከአደጋው በኋላ ከኤንዲ ቲቪ ጋር ቃለምልልስ ያደረገችው ቦሆሚ ቻውሃን የእረፍት ጊዜዋን አህመዳባድ ከሚገኙ ቤተሰቦቿ ጋር አሳልፋ በበረራ ቁጥር 171 ለመብረር ትኬት ቆርጣ ነበር።
ሆኖም ወደ አውሮፕላን ማረፊያው እያመራች በነበረበት ወቅት ከፍተኛ የትራፊክ መጨናነቅ እንዳጋጠማት እና አስር ደቂቃ ዘግይታ አህመዳባድ አየር ማረፊያ ስትደርስ ግን ወደውስጥ እንዳትገባ በመከልከሏ መናደዷን ገልፃለች።
ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላም እዛው አየር መንገዱ ውስጥ እያለች ወደለንደን ልትጓዝበት የነበረው አውሮፕላን መከስከሱን ማየቷን ተናግራለች።
ኢቢሲ
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።