ማሻ ፣ የግንቦት 02፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) ዕውቀት ችግር እስካልፈታ ድረስ በዕውቀት መስፈርት ውስጥ ሊታይ የሚያስችል ብቃት አይኖረውም።
በኢትዮጵያ እስከ ቀጣይ ዓመት ድረስ በአጠቃላይ ወደ 55 ቢሊየን ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት እየተደረገ ነው፤ ይህም ይህም በዓለም ላይ ትልቁ የደን ማልማት ሥራ ይሆናል፡፡
ከሌሎች ሴክተሮች ዕቅድ አንጻር ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ሙሉ በሙሉ ተሳክቷል፡፡ አሁን ላይ ለዲጂታል 2030 ዝግጅት እየተደገ ነው፡፡
በሀገራችን ቴክኖሎጂ በሲቪል ሰርቪስ፣ በሕግ ማስከበር፣ በመከላከያ፣ በሚዲያ፣ በግብርና፣ በኢንዱስትሪ ዘርፎች ያሉ ሥራዎችን ለማሳካት እና ለማሳለጥ ጥቅም ላይ እዋለ ነው፡፡
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በዓመት ከ100 ሚሊየን በላይ መንገደኞችን ማጓጓዝ የሚያስችል ዕቅድ እና ለዚህም የሚያግዘውን አዲስ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ለመገንባት እየሠራ ነው፡፡
በመከላከያ ሠራዊት ውስጥ ሎጂስቲክስ የሚያጓጉዙ ድሮኖች እንዲሁም በሰው ሠራሽ አስተውሎት (ኤ አይ) የሚንቀሳቀሱ ተዋጊ ጀቶች ጥቅም ላይ እየዋሉ ይገኛሉ።
ከዓመታት በፊት የኢትዮ ቴሌኮም አገልግሎት በአፍሪካ በጣም ውድ ነበር፤ አሁን ላይ ግን በአህጉሪቱ በዝቅተኛ ዋጋ አገልግሎቱን ማቅረብ ተችሏል፡፡
በአሁኑ ወቅት 51 ሚሊየን ገደማ ሰዎች የሞባይል ፋይናንስ አገልግሎት ተጠቃሚ ሆነዋል፡፡
የሰው ሠራሽ አስተውሎት(አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ – ኤ አይ) አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ በፒኤችዲ ደረጃ መሰጠት ተጀምሯል።
በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ከ“ቻት ጂፒቲ” ወይንም “ዲፕ ሲክ” ጋር ተመሳሳይነት ያለው “መላ” የተሰኘ የሀገር ውስጥ ቋንቋን በስፋት የሚጠቀም የኤአይ ሥርዓት ተገንብቷል፡፡
የአፍሪካ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (ኤአይ) ሰሚት በአዲስ አበባ ከተማ ይካሄዳል። በዚሁ ወቅት 1 ሺህ ገደማ ድሮኖች በኤአይ ታግዘው ትርዒት ያቀርባሉ፡፡
የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ በአፍሪካ ውስጥ ቀዳሚ ሚና አለው፡፡ እንደ ኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ኢትዮ ቴሌኮም ሁሉ የአፍሪካውያን ኩራት መሆን ይችላል።
ፋና
More Stories
የማህበራዊ ሚዲያው ተፅዕኖ የጎላበት ምህዳር ተፈጥሯል- የክልሉ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሃላፊ አቶ የሺዋስ አለሙ።
የሚዲያና ኮሚኒኬሽን ባለሙያዎች ተልዕኮቸውን በሀላፍነት እና በዕውቀት እንዲወጡ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድሩ ዶክተር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ አሳሰቡ።
የደቡብ ምዕራብ ሚዲያ ኔትወርክ በድህረገጽና በማህበራዊ ሚዲያ ዘርፍ የሥራ ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር በታርጫ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።