ማሻ ፣ የግንቦት 02፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) ዕውቀት ችግር እስካልፈታ ድረስ በዕውቀት መስፈርት ውስጥ ሊታይ የሚያስችል ብቃት አይኖረውም።
በኢትዮጵያ እስከ ቀጣይ ዓመት ድረስ በአጠቃላይ ወደ 55 ቢሊየን ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት እየተደረገ ነው፤ ይህም ይህም በዓለም ላይ ትልቁ የደን ማልማት ሥራ ይሆናል፡፡
ከሌሎች ሴክተሮች ዕቅድ አንጻር ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ሙሉ በሙሉ ተሳክቷል፡፡ አሁን ላይ ለዲጂታል 2030 ዝግጅት እየተደገ ነው፡፡
በሀገራችን ቴክኖሎጂ በሲቪል ሰርቪስ፣ በሕግ ማስከበር፣ በመከላከያ፣ በሚዲያ፣ በግብርና፣ በኢንዱስትሪ ዘርፎች ያሉ ሥራዎችን ለማሳካት እና ለማሳለጥ ጥቅም ላይ እዋለ ነው፡፡
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በዓመት ከ100 ሚሊየን በላይ መንገደኞችን ማጓጓዝ የሚያስችል ዕቅድ እና ለዚህም የሚያግዘውን አዲስ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ለመገንባት እየሠራ ነው፡፡
በመከላከያ ሠራዊት ውስጥ ሎጂስቲክስ የሚያጓጉዙ ድሮኖች እንዲሁም በሰው ሠራሽ አስተውሎት (ኤ አይ) የሚንቀሳቀሱ ተዋጊ ጀቶች ጥቅም ላይ እየዋሉ ይገኛሉ።
ከዓመታት በፊት የኢትዮ ቴሌኮም አገልግሎት በአፍሪካ በጣም ውድ ነበር፤ አሁን ላይ ግን በአህጉሪቱ በዝቅተኛ ዋጋ አገልግሎቱን ማቅረብ ተችሏል፡፡
በአሁኑ ወቅት 51 ሚሊየን ገደማ ሰዎች የሞባይል ፋይናንስ አገልግሎት ተጠቃሚ ሆነዋል፡፡
የሰው ሠራሽ አስተውሎት(አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ – ኤ አይ) አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ በፒኤችዲ ደረጃ መሰጠት ተጀምሯል።
በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ከ“ቻት ጂፒቲ” ወይንም “ዲፕ ሲክ” ጋር ተመሳሳይነት ያለው “መላ” የተሰኘ የሀገር ውስጥ ቋንቋን በስፋት የሚጠቀም የኤአይ ሥርዓት ተገንብቷል፡፡
የአፍሪካ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (ኤአይ) ሰሚት በአዲስ አበባ ከተማ ይካሄዳል። በዚሁ ወቅት 1 ሺህ ገደማ ድሮኖች በኤአይ ታግዘው ትርዒት ያቀርባሉ፡፡
የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ በአፍሪካ ውስጥ ቀዳሚ ሚና አለው፡፡ እንደ ኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ኢትዮ ቴሌኮም ሁሉ የአፍሪካውያን ኩራት መሆን ይችላል።
ፋና
More Stories
ቻይና የመጀመሪያውን አብራሪ አልባ የአየር ታክሲ ትራንስፖርት ይፋ አደረገች
26 ጎማዎች ያሉት የዓለማችን ረዥሙ መኪና
በ2030 በአለም አቀፍ ደረጃ ከ93 ሚሊየን በላይ ሰራተኞች በሰው ሰራሽ አስተውሎት እንደሚተኩ ሪፖርት አመላከተ