ማሻ ፣ የመጋቢት 29፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) የፓስፖርት አገልግሎት ደንበኞችን በማጭበርበር ወንጀል የተጠረጠሩ ሁለት ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አስታውቋል፡፡
ከአገልግሎቱ የተገኘው መረጃ እንዳመለከተው ተጠርጣሪዎቹ አስቸኳይ ፓስፖርት እናሰራላችኋለን የሚል ማታለያ በመጠቀም በ24 የአገልግሎቱ ደንበኞች ላይ የማጭበርበር ወንጀል መፈጸማቸው ተጠቅሷል፡፡
የወንጀል ድርጊቱን ፈፅመዋል የተባሉት ተጠርጣሪዎች ተቋሙ ለ5 ቀን 20 ሺህ ብር የሚያስከፍለውን 28 ሺህ ብር ሲያስከፍሉ መቆየታቸውም ነው የተገለፀው፡፡
አገልግሎቱ ከፌደራል ፓሊስ እና ከአዲስ አበባ ፖሊስ ጋር በቅንጅት ባደረገው ክትትል ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር ውለው፣ ተገልጋዮቹ የከፈሉት ገንዘብ እንዲመለስ መደረጉ ተመላክቷል፡፡
ደንበኞች ከመሰል የማጭበርበር ተግባር ራሳቸውን እንዲጠብቁ እንዲሁም ስለአገልግሎቱ ማንኛውም አይነት መረጃ ከኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የመረጃ ዴስክ አልያም ከተቋሙ የማህበራዊ ትስስር ገጾች እንዲያገኙ አገልግሎቱ አሳስቧል፡፡
ኢቢሲ
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።