በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ከታክስ ዕዳ ከ49 ቢሊየን ብር በላይ መሰብሰቡን ገቢዎች ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
ከታክስ ዕዳ 41 ቢሊየን 662 ሚሊየን 896 ሺህ 213 ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ 49 ቢሊየን 664 ሚሊየን 299 ሺህ 370 ብር መሰብሰቡን ሚኒስቴሩ አስታውቋል፡፡
ከፍተኛ የታክስ ዕዳ መጠን ያለባቸውን ታክስ ከፋዮች በመለየት ቅድሚያ ተሰጥቶ መሠራቱና ለዋና መስሪያ ቤት በልዩ ሁኔታ እንዲታዩ የሚቀርቡ ጥያቄዎችን ፈጥኖ ምላሽ መስጠቱ ለዕቅዱ መሳካት ማገዙ ተገልጿል፡፡
ከተሰበሰበው የታክስ ዕዳ ውስጥ 30 ቢሊየኑ 30 ቀን ካልሞላው የታክስ ዕዳ መሰብሰቡን የሚኒስቴሩ መረጃ አመላክቷል፡፡
FBC
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።