የቀዳማዊት እመቤት ጽሕፈት ቤት ከጉድ ኔበርስ ዓለም አቀፍ በጎ አድራጎት ድርጅት ጋር በጋራ ለመሥራት የሚያስችል የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል።
ዋናው መቀመጫው እና የተመሠረተበት ሀገር ደቡብ ኮሪያ ከሆነው ጉድ ኔበርስ ዓለም አቀፍ በጎ አድራጎት ድርጅት ጋር በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት መደረሱን የቀዳማዊት እመቤት ጽሕፈት በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ባሰፈርው መልዕክት አስታውቋል።
ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በመልዕክቱ እንደገለጹትም፤ ከበጎ አድራጎት ድርጅቱ ጋር በፅሕፈት ቤታቸው እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎችን ለመደገፍ እና በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን ውይይት አድርገዋል።
በውይይቱም ወደ ስራ የሚያስገባ የመግባቢያ ሰነድ መፈራረማቸውን ነው ቀዳማዊት እመቤቷ የጠቀሱት፡፡
EBC
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።