

በርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ የተመራው የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ወደ ኦሞ ኩራዝ ቁጥር 3 ስኳር ፋብሪካ የስራ እንቅስቃሴን ለመመልከት በስፍራው ተገኝተዋል ።
በጉብኝቱ ርዕሰ መስተዳድሩን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣የምዕራብ ኦሞና ካፋ ዞን አመራሮች የተገኙ ሲሆን የኢትዮጵያ ስኳር እንዱስትሪ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ወዮ ሮባ እና የፋብሪካዉ አመራሮች አቀባበል አድርጎላቸዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩና ልዑካቸዉ ሁለት ቀን በሚኖራቸዉ ቆይታ የፋብሪካዉን የስራ ዕንቅስቃሴ፣የእርሻ ሁኔታ እና የምርት ሂደት እንዲሁም በምዕራብ ኦሞ ዞን እየተሰሩ ያሉ የመንገድና የኢንቨስትመት ፕሮጀክቶች በመጎብኘት በነገው ዕለት ከሚመለከታቸዉ አካላት ጋር ውይይት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል ሲል የዘገበው የክልሉ የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ነው።
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።