ማሻ ፣ የግንቦት 03፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) የዩክሬን ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዜሌንስኪ ሩስያ ለቀጥታ የሰላም ንግግሮች ያቀረበችውን ሀሳብ በደስታ በመቀበል ነገር ግን ድርድር ከመጀመሩ በፊት የተኩስ አቁም መኖር እንዳለበት አጥብቀው አሳስበዋል።
ዘሌንስኪ በኤክስ ገፃቸው ላይ፥ የሩስያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን የቀጥታ ውይይት ለመጀመር ያቀረቡትን ጥሪ “በጎ ምልክት” በማለት ገልፀውታል።
አያይዘውም፥ “መላው ዓለም ይህን ለረጅም ጊዜ ሲጠብቀው ቆይቷል” ብለዋል።
ሆኖም ግን ማንኛውንም ግጭት ለማስቆም የመጀመሪያው እርምጃ መሆን ያለበት የተኩስ አቁም ስምምነት ነው ብለዋል።
ኢቢሲ
More Stories
አሜሪካ እና ቻይና የገቡበትን የታሪፍ ሰጣ ገባ ማርገብ የሚያስችል ውይይት አደረጉ
አሜሪካዊው ሮበርት ፕሪቮስት የሮማ ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ሆነው ተመረጡ
አራተኛው ዙር የኢራን እና የአሜሪካ ድርድር ላልተወሰነ ጊዜ ተላለፈ