ማሻ ፣ የግንቦት 03፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) የዩክሬን ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዜሌንስኪ ሩስያ ለቀጥታ የሰላም ንግግሮች ያቀረበችውን ሀሳብ በደስታ በመቀበል ነገር ግን ድርድር ከመጀመሩ በፊት የተኩስ አቁም መኖር እንዳለበት አጥብቀው አሳስበዋል።
ዘሌንስኪ በኤክስ ገፃቸው ላይ፥ የሩስያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን የቀጥታ ውይይት ለመጀመር ያቀረቡትን ጥሪ “በጎ ምልክት” በማለት ገልፀውታል።
አያይዘውም፥ “መላው ዓለም ይህን ለረጅም ጊዜ ሲጠብቀው ቆይቷል” ብለዋል።
ሆኖም ግን ማንኛውንም ግጭት ለማስቆም የመጀመሪያው እርምጃ መሆን ያለበት የተኩስ አቁም ስምምነት ነው ብለዋል።
ኢቢሲ
More Stories
የአውሮፓ ህብረት ያወጣቸውን ደንቦች መሠረት በማድረግ የግብርና ምርቶች ከደን ጭፍጨፋ ነፃ ሆነው እንዲመረቱ ከማድረግ አንፃር የግብርና ባለሙያዎች ሚና የጎላ እንደሆነ ተገለፀ ።
ትራምፕ ቲክ ቶክን የሚገዙ የአሜሪካ ባለሀብቶች ማግኘታቸውን ገለፁ
ሩሲያ እና ህንድ በጦር መሳሪያ አቅርቦት ላይ ያላቸውን ትብብር ለማሳደግ እንደሚሰሩ አስታወቁ፡፡