ማሻ ፣ የግንቦት 03፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) የዩክሬን ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዜሌንስኪ ሩስያ ለቀጥታ የሰላም ንግግሮች ያቀረበችውን ሀሳብ በደስታ በመቀበል ነገር ግን ድርድር ከመጀመሩ በፊት የተኩስ አቁም መኖር እንዳለበት አጥብቀው አሳስበዋል።
ዘሌንስኪ በኤክስ ገፃቸው ላይ፥ የሩስያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን የቀጥታ ውይይት ለመጀመር ያቀረቡትን ጥሪ “በጎ ምልክት” በማለት ገልፀውታል።
አያይዘውም፥ “መላው ዓለም ይህን ለረጅም ጊዜ ሲጠብቀው ቆይቷል” ብለዋል።
ሆኖም ግን ማንኛውንም ግጭት ለማስቆም የመጀመሪያው እርምጃ መሆን ያለበት የተኩስ አቁም ስምምነት ነው ብለዋል።
ኢቢሲ
More Stories
አሜሪካ በኢራን ላይ የአየር ጥቃት ፈፀመች
አሜሪካ በኢራን ላይ አዲስ የአየር ጥቃት ፈፀመች
በ24 ሰዓት ውስጥ 25 መርከቦች በሆርሙዝ ሰርጥ አልፈዋል – ኢራን