ማሻ ፣ የሚያዝያ 24፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) የሸካ ዞን ጤና መምሪያ የኩፍኝ በሽታን ለመከላከል የሚያስችል ክትባት ለመስጠት ለሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ስልጠና እየሰጠ ነዉ።
በሸካ ዞን ጤና መምሪያ የእናቶችና ህጻናት ጤናና ስርዓተ ምግብ ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ተገኝ ገቦ ከግንቦት ስድስት እስከ አስራ አምስት ቀን 2017 ዓ.ም ለተከታታይ 10 ቀናት እድሜያቸው ከዘጠኝ ወር እስከ አምስት አመት ለሆናቸዉ ህጻናት የኩፍኝ በሽታን መከላከያ ክትባት እንደሚሰጥ ገልጸዋል።
ይህንንም ክትባት በአስፈላጊው ሁነታ ለማዳረስ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸው የተገለጽ ሲሆን ከነዚህም አንዱ እየተሰጠ ያለዉ የአሰልጣኞች ስልጠና መሆኑ ተመላክቷል።
እ.አ.አ በ2023 በተደረገዉ ጥናት በአለማችን እድሜያቸው ከ15 አመት በታች የሆኑና የኩፍኝ በሽታ ክትባት ያልወሰዱ ህጻናት 95 በመቶ በሽታ ላይ እንደሚወድቁ የሸካ ዞን ጤና መምሪያ የክትባት ፕሮግራም አስተባባሪ አቶ ገረመው ጭቶ ስልጠና በሰጡበት ወቅት ገልጸዋል።
በዚህ የክትባት ጊዜ ዉስጥ በዞኑ ባሉ እድሜያቸው ከ5 አመት በታች የሆኑ 41ሺህ 47 ህጻናትን ለመከተብ መታቀዱም ተመላክቷል።
የኩፍኝ በሽታ ለተለያዩ በሽታዎች ከማጋለጥ ባሻገር እስከሞት ድረስ የሚያደርስ መሆኑን ወላጆች በመገንዘብ ልጆቻቸውን እንዲያስከትቡም ጥሪ አቀርቧል።
ለሶስት ቀናት በሚሰጠው ስልጠና ላይ የሁሉም መዋቅር የጤና ጽ/ቤት ሀላፊዎች፣ በዘርፉ የጤና ባለሙያዎች፣ እንድሁም የዞን ጤና ማናጅመንት አባላትና ለሎች ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛሉ።
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።