የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ዶ/ር የተመራው ልዑክ ለይፋዊ ስራ ጉብኝት ኮንታ ዞን ገብቷል።
ልዑኩ ወደ ኮንታ ዞን ሲደርስ የኮንታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታከለ ተስፉን ጨምሮ ሌሎች የዞን፣የአመያ ከተማ አስተዳደር የመንግስትና የፓርቲ ከፍተኛ ስራ ኃላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ በዞኑ አመያ ዙሪያ ወረዳ ሼታ ጫሬ ቀበሌ በ105 ሄ/ር ላይ የለማውን የባቄላ ማሳ የጎበኙ ሲሆን በቆይታቸው ሌሎች በዞኑ ውስጥ እየተሰሩ ያሉ የልማት ስራዎችን ይጎበኛሉ ተብሎም ይጠበቃል።
More Stories
የደቡብ ሬድዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የማሻ ቅርንጫፍ ጣቢያ በመምህር ዳኪቶ ጋወቶ ድንገተኛ ህልፈት የተሰማዉን ጥልቅ ሀዘን ገለፀ።
ማንቼስተር ዩናይትድ አርሰናልን በገዛ ሜዳው አሸነፈ
መልካም አብነቶች በማስፋት ወደ ብልጽግና የሚደረገውን ጉዞ እናፋጥናለን – ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)