በኦሮሚያ ክልል መንግስት እና የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት የሰላም ስምምነት በመፈጸማቸው የሰራዊቱ አባላት ወደ ካምፕ መግባት መጀመራቸው ይታወቃል።የኦሮሚያ ክልል የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የተደረሰውን የሰላም ስምምነት አስመልክቶ በሰጠው መግለጫ፤ የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት የሰላም አማራጭን በመቀበሉ ከፍተኛ ደስታ እንደተሰማው ገልጿል።በጫካ የቀሩ የሰራዊቱ አባላትም ፈጥነው ወደ ሰላማዊ አማራጭ እንዲመጡም ጥሪውን አስተላልፏል።ሰላም እንዲሰፍን የሃይማኖት አባቶች ጸሎት እና ምህላን ሲያደርጉ እንደነበር ያስታወሰው መግለጫው፤ በቀጣይነትም ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ጉባኤው የሰላም ግንባታ ላይ አበክሮ እንደሚሰራ አረጋግጧል።
ፋና
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።