ትራምፕ በመጪው ህዳር ለሚካሄደው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ በፔንሲልቬንያ የምረጡኝ ቅስቀሳ ሲያካሂዱ ነው የግድያ ሙከራ የተደረገባቸው። በደጋፊዎቻቸው መሃል በመድረክ ላይ ቆመው የምረጡኝ ቅስቀሳ ሲያሰሙ የተተኮሰባቸው ዶናልድ ትራምፕ፤ በጆሯቸው አካባቢ ጉዳት እንደደረሰባቸው የተለቀቁ ምስሎች አሳይተዋል። በወቅቱ በነበረው የተኩስ ልውውጥ የግድያ ሙከራውን ያደረገው ግለሰብ ህይወት ማለፉ ተነግሯል።ሁለት ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድ ጉዳት መድረሱን የአሜሪካው ኤንቢሲ ኒውስ ዘግቧል።ዶናልድ ትራምፕ በመልካም ጤንነት ላይ ናቸው ተብሏል። የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ክስተቱን ተከትሎ በሰጡት መግለጫ ጥቃቱን አውግዘዋል።አሜሪካ ውስጥ በኃይል የሚደረግ እንቅስቃሴ ቦታ የለውም ሲሉም ተናግረዋል።ሌሎች የሀገሪቱ ባለስልጣናትና የዓለም ሀገራት መሪዎችም ጥቃቱን እያወገዙ መሆኑ ተዘግቧል።
EBC
More Stories
አሜሪካ በኢራን ላይ የአየር ጥቃት ፈፀመች
አሜሪካ በኢራን ላይ አዲስ የአየር ጥቃት ፈፀመች
በ24 ሰዓት ውስጥ 25 መርከቦች በሆርሙዝ ሰርጥ አልፈዋል – ኢራን