የኢራን የሀገርውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር ለሀገሪቱ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ የሚወዳደሩ 6 እጩዎችን ይፋ አድርጓል፡፡
ሚኒስቴሩ በዚህ ወር በሚካሄደው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ የሚወዳደሩ የስድስት እጩዎችን የመጨረሻ ዝርዝር ነው ይፋ ማድረጉ የተሰማው፡፡
ፕሬዚዳንታዊ ምርጫው በቅርቡ የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ኢብራሂም ራይሲ በሄሊኮፍተር አደጋ ህይዎታቸው ማለፉን ተከትሎ ለሀገሪቱ አዲስ ፕሬዚዳንት መምረጥ በማስፈለጉ ነው የሚካሄደው፡፡
ለፕሬዚዳንትነት ከሚወዳደሩት እጩዎች መካከል በሀገሪቱ በምክትልፕሬዚዳንትነት እያገለገሉ የሚገኙትን አሚርሆሴይን ቃዚዛዴህ ሃሺሚን ን ጨምሮ በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች እያገለገሉ ያሉ ሃላፊዎች እንደሚገኙበት የአርቲ ዘገባ አመላክቷል፡፡
FBC
More Stories
እየተጠናከረ የመጣው የብሪክስ ሀገራት ግንኙነት…
አሜሪካ ሶሪያን አጠቃች
የሩሲያ ጦር በፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን መኖሪያ ቤት ላይ ተፈጽሟል ላለው ጥቃት አፀፋ በዩክሬን ላይ መጠነ ሰፊ ጥቃት መፈጸሙን አስታውቋል።