የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ በኳታር ዶሃ የሚገኘው የዶክ ሕክምና ማዕከል መስራች በሆኑት ዶ/ር ኢማኑኤል ቶሎሳ ከተመራ የልዑካን ቡድን አባላት ጋር ተወያይተዋል። የሕክምና ማዕከሉ በኢትዮጵያ የጤና ዘርፍ በኢንቨስትመንት መሰማራት በሚችልበት ሁኔታ ላይ የሀሳብ ልውውጥ ተደርጓል።ማዕከሉ በዓይነቱ ልዩ የሆነ እና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፈ የአጥንት ህክምና ማዕከል በኢትዮጵያ ለማቋቋም ፍላጎት እንዳለው ተገልጿል። ዶክ በኳታር ከኦርቶፔዲክ፣ ሩማቶሎጂ፣ ኒውሮሎጂ፣ ኒውሮፊዚዮሎጂ፣ ፊዚዮቴራፒ፣ ካይሮፕራክቲክ እና የጥርስ ሕክምና ጋር የተያያዙ የምርምራ እና የሕክምና አገልግሎቶችን የሚሰጥ ትልቁ የጤና ማዕከል መሆኑን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
EBC
More Stories
” የፕሬስ ነጻነት ቀን ስናከብር ዜጎች በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) መረጃ እንዳይጭበረበሩ ትክክለኛ መረጃ የሚያገኙበት እሳቤ የሚያጎላበት ቀን ሊሆን ይገባል፡፡”
አራተኛው ዙር የኢራን እና የአሜሪካ ድርድር ላልተወሰነ ጊዜ ተላለፈ
የደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የስራ ኃላፊዎች የማሻ ቅርንጫፍ ጣቢያ የስራ አፈጻጸምን ተመለከቱ