የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ትምህርት ቢሮ የትምህርት አስተዳደር መረጃ ስረዓት ዲጂታላይዘሽን ላይ ያተኮረ የግምገማ መድረክ እየተካሄደ ነዉ።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ትምህርት ቢሮ ምክትል የቢሮ ኃላፊና የመማር ማስተማርና ምዘና ዘርፍ ኃላፊ ደስታ ገነሜ(ዶ/ር) ጥራት ያለዉ መረጃ ስረዓት በትምህርት ስረዓቱ ላይ ያለዉን ጉድለት ለመሙላት ጉልህ ሚና እንዳለው ተናግረዋል ።
የትምህርት ጥራት አመላካች ከሆኑ ተግባራት መካከል አንዱ የትምህርት መረጃ ስረዓት መሆኑን ገልፀዉ በየደረጃው ያሉት አካላት የትምህርት መረጃ በጥራት መሙላት እንዳለባቸው አሳስበዋል ።
በባለፉት ግዜያት በማኑዋል ስሰራ የነበረዉ የመረጃ ስረዓት ኦንላይን መደረጉን ተናግረው ይህም ጥራት ያለዉን የትምህርት መረጃ ለማደረጀት አይነተኛ ሚና እንደሚወጣ ገልፀዉ ለዚህም ርዕሰ መምህራን ድርሻቸዉ መወጣት ይገባቸዋል ብለዋል።
የመምህራን ፣የተማርዎች ፣የትምህረት ቤቶች መረጃና የጎልማሶች መሰረታዊ ትምህርት መረጃ በትክክል ከመመዝገብ አንፃር የሚታዩ ክፍተቶች ማረም እንደሚገባ ገልጸዋል ።
በመድረኩ የቢሮዉ የትምህርት አመራር መረጃ ስረዓት ቡድን አቶ ታጠቅ ታደሰ በኩል ሰነድ እየቀረበ ይገኛል።
ጥራት ያለዉ መረጃ ስረዓት በትምህርት ስረዓቱ ላይ ያለዉን ጉድለት ለመሙላት ጉልህ ሚና እንዳለው ተገለፀ
More Stories
አሜሪካ ለኢራን ፍልሚያ ተጨማሪ 200 ቢሊዮን ዶላር ጠየቀች!
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮምሽነር ዶክተር ካሳ ለ1,447ኛዉ ለኢድ አልፈጥር በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በሸካ ዞን የፓርቲና የልማት ስራዎች አፈጻጸም እየተገመገመ ነዉ