March 5, 2026

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

ኤች አይ ቪ ኤድስን በመከላከልና በመቆጣጠር በዜጎች ማህበራዊ ሕይወት ላይ ተጽእኖ እንዳያሳድር በማድረግ ክልላዊና  ሀገራዊ ግቦችን ማሳካት እንደሚገባ ተገለፀ ።

የደ/ም/ኢ/ህ/ ክልል  ጤና ቢሮ በሸካ ዞን ኤች አይ ቪ መከላከልና መቆጣጠር ዙሪያ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን  የመስክ ምልከታ አካሄዷል ።

በHIV AIDS በሽታን በመከላከልና በመቆጣጠር ዙሪያ የህብረተሰቡን ግንዛቤ በማሳደግ የአምራች ዜጎችን ህይወት መታደግ የሁሉም ድርሻ መሆን እንዳለበትም ተመላክቷል ።

የመስክ ምልከታ ቡድን ከዞን ጤና መምሪያ ባለሙያዎች ጋር በመሆን በየኪ ወረዳ በጪ፣በአንድራቻ ወረዳ ጌጫና በማሻ ከተማ አስተዳደር የማሻ ጤና ጣቢያዎች የHIV AIDS በሽታን ለመከላከልና ለመቆጣጠር እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ዙራያ የመስክ ምልከታ አካሂዶ ጠንካራና መሻሻል ያለባቸዉ  ጉዳዮችን በመለየት  ግብረ መልስ ሰጥቷል ።

የማሻ ጤና ጣቢያ የHIV AIDS በሽታን ለመከላከልና ለመቆጣጠር እያተከናወነዉ ያለዉ ተግባር  ጥሩ ተሞክሮ ሊሆን እንደሚችል የጠቆሙት በክልሉ ጤና ቢሮ የHIV AIDS በሽታን መከላከልና መቆጣጠር በCDC ፕሮጀክት የHIV Care and Treatment Adviser ዶክተር እመቤት ከተማ የHIV ጥንቃቄና እንክብካቤ እንድሁም  የVCT አግልግሎት ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል ።

ከ0.5% የAIDS  ፈንድ 925,000 ብር ተሰብስቦ ኦዲት እየተደረገ ለ8  ሰዎች ቫይረሱ በደማቸዉ ለሚገኘዉ ወገኖች እየተከፈለ መሆኑ  በጠንካራ ጎን የሚታይ ነዉ  ሲሉ በክልሉ ጤና ቢሮ የHIV AIDS መከላከልና መቆጣጠር ስራ ሂደት የCDC ፕሮጀክት የHIV ምርመራ አማካሪና የMTCT ፎካል  አቶ  የኋላሼት ተመዝገን ተናግረዋል

በሌላ በኩል  የክልኒካል ኦፊሰር ያለመኖር፣የኮንዶም ስርጭት ዝቅተኛ መሆንና የተሰሩ መረጃዎችን በወቅቱ ሪፖርት ከማድረግ አንፃር ያሉ ክፍተቶች እንድሁም HIV ከእናት ወደ ልጅ  እንዳይተላለፍ በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ አስገንዝበዋል ።

የማሻ ከተማ ጤና ጥበቃ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ኢሌሳ መኮንን በክልሉ ጤና ቢሮ የተደረገዉን የመስክ ምልከታ አድንቀዉ፡የታዩ ጠንካራ ጎኖችን በማስቀጠልና ክፍተቶችን ለማረም በትኩረት እንሰራለን ብለዋል ።

በተለይ የHIV AIDS ምርመራ ለማድረግ ማነቆ የሆኑ የባለሙያና የግባት እጥረት ለሟሟላት ከባለድርሻ አካላት ጋር በትኩረት እንደሚሰራ ገልፆ ክልሉም በስልጠና እንዲያግዛቸዉ መልዕክት አስተላልፈዋል ።