February 16, 2026

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

የኢትዮጵያ ውሹ ብሔራዊ ቡድን 6ሜዳሊያዎችን በማስመዝገብ ወደ ሀገሩ ተመለሰ።

ብሔራዊ ቡድኑ ቦሌ አለም አቀፍ አየር መንገድ ሲደርስ በባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የስፖርት ልማት መሪ ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ አበባ አማረ እና በፌዴሬሽኑ ምክትል ፕሬዚዳንት አቡበክር አህመድ አቀባበል ተደርጎለታል።

በግብፅ ካይሮ በተካሄደው 7ኛው የአፍሪካ ውሹ ጁኒየር ሻምፒዮና ላይ የተሳተፈው የኢትዮጵያ ውሹ ብሔራዊ ቡድን 6 ሜዳሊያዎችን ማስመዝገብ ችሏል።

ብሔራዊ ቡድኑ በሻምፒዮናው 4 ብር እና 2 ነሀስ በድምሩ 6 ሜዳዮችን በማስመዝገብ ውድድሩን አጠናቋል፡፡

ብሔራዊ ቡድኑ በሻምፒዮናው ሲሳተፍ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው።