February 10, 2026

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

የብሔረሰቦችን ቋንቋ፣ ባህል እና መልካም ዕሴቶች እንዲጎለብቱ ማድረግ ለልማትና ለሰላም ዕሴት ግንባታ ያለው ፍይዳ የጎላ ነው ተባለ

ማሻ፤ የካቲት 3/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) ከየካቲት 4 እስከ 5 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚከበረዉ የማጃንግ ብሔረሰብ  ቋንቋና ባህል ሲምፖዚየም  የቅድመ ዝግጅት ስራዎች መጠናቀቃቸውተገልጿል ።

የበዓሉን ቅደመ ዝግጅት ስራዎች በማስመልከት መግለጫ የሰጡት የማጃንግ  ቋንቋና ባህል ሲምፖዚየም  ሰብሳቢ  አቶ ዮሐንስ በንዲ እንደገለጹት ከየካቲት 4 እስከ 5 ቀን 2018 ዓ.ም በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ  ለሚከበረዉ የማጃንግ ብሔረሰብ  ቋንቋና ባህል ሲምፖዚየም የቅድመ ዝግጅት ስራዎች መጠናቀቃቸውን ገለጸዋል ።

የበዓሉ መከበር የብሔረሰብን ባህል፣ታሪክ፣እና ቋንቋን ከማሳደግ ባለፈ ለልማት እና ለሰላም ዕሰት ግንባታ የሚያበረክተው አስተዋጽኦ የጎላ መሆኑን የገለፁት አቶ ዮሐንስ ይህንኑ ይበልጥ ለማጠናከር ይሰራል  ብለዋል ።

ለረጅም ዓመታት ተዘንግተው የቆዩ የማጃንግ ብሔረሰብ ባህላዊ እሴቶችንና የአኗኗር ዘይቤዎችን እንደገና ለማነቃቃት ያለመ ሲምፖዚየም መሆኑንም ጭምር አቶ ዮሐንስ ጠቁመዋል ።

ከየካቲት 4 እስከ 5 ቀን 2018 ዓ.ም በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ በሚከበረዉ የማጃንግ ብሔረሰብ  ቋንቋና ባህል ሲምፖዚየም ላይ የባህል ትርኢቶች ፣ የምግብ አውደ ርዕይን ጨምሮ የማጃንግ ቋንቋና ባህልን የሚዳስሱ ጥናታዊ ጽሑፎች ቀርበው ውይይቶች እንደሚደረጉ ጠቁመዋል ።

በሲምፖዚየሙ ላይ ከጋምቤላ፣ ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የብሔረሰቡ ተወላጆችና ተጋባዥ  እንግዶች ፣ የዩኒቨርሲቲ ምሁራንን ጨምሮ ፣የሌሎች ብሔረሰቦች ተወካዮች እንደሚሳተፉ ተገልጿል