ማሻ፣ ጥር 03/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍኤም 103.8) አሜሪካ በሶሪያ በሚገኘው እስላማዊ መንግስት ብላ በምትጠራው ላይ ከባድ ጥቃት ፈፀመች ተባለ።
ጥቃቱ የተፈጸመው ባለፈው ወር በሶሪያ ፓልሜራ በአሜሪካ ወታደሮች ላይ ለደረሰው ጉዳት የበቀል ምላሽ ነው ስትል ዋሽንግተን አስታውቃለች።
የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ እንዳስታወቀው ፣ አይ አይ ኤስ ላይ መጠነ ሰፊ ጥቃት አድርሷል።
ዘመቻ ሀውክአይ በተሰኘው ትራምፕ መራሽ ጥቃት አይ ኤስ ሲጠቀምበት የነበረው የጦር መሳሪያ መውደሙን ማዕከላዊ ዕዙ አክሎ ገልጿል።
አይ ኤስ ላይ የተወሰደው እርምጃ ለወደፊቱ ቡድኑ ለሚያደርገው ጥቃት ከባድ አጸፋ እንደሚጠብቀው ለማስጠንቀቅ ነው ሲሉ የዋሽንግተን ባለስልጣናት ተናግረዋል።
በአሜሪካ ጦር እና ተባባሪዎች ላይ የሚደርስ ጥቃት መልሱ የከፋ መሆኑን አይ ኤስ እና ሌሎች ቡድኖች ማወቅ አለባቸው ሲል ማዕከላዊ ዕዙ በኤክስ ገፁ ላይም አስፍራሯል ሲል ታይምስ ኦፍ ኢንዲያን ጠቅሶ ኤን ቢሲ ኢትዮጵያ ዘግቧል።
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።