የሶማሊያ ፌደራል ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼኽ ሞሃሙድ ለአንድ ቀን ይፋዊ የሥራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገብተዋል።
ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼኽ ሞሃሙድ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተቀብለዋቸዋል።
“ባለፈው አንድ ዓመት እየሰራንባቸው የቆየነውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ውይይቶች በመቀጠል ፍሬያማ ውይይት አድርገናል” ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባጋሩት መልዕክት።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ “የሃሳብ ልውውጣችን የወል የቅድሚያ ጉዳዮቻችንን ለመከወን ብሎም ለጠንካራ ግንኙነት፣ ቀጠናዊ መረጋጋት እና ልማት ያለንን ቁርጠኝነት በድጋሚ ያፀና ነበር” ማለታቸው ተዘግቧል።
More Stories
የገና በዓል አከባበር በተለያዩ የዓለም ክፍሎች…
ሙስናና ብልሹ አሰራሮች የመከላከሉ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግሥት የስነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን አስታውቀ
በክልሉ ህገወጥ ንግድ፣ ዋጋ ንረት እንዲሁም የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴዎችን ለመግታት በየደረጃው ሥራዎችን በልዩ ትኩረት መምራትና መከታተል ያስፈልጋል -ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር