December 25, 2025

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼኽ ሞሃሙድ ጋር ተወያዩ

የሶማሊያ ፌደራል ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼኽ ሞሃሙድ ለአንድ ቀን ይፋዊ የሥራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገብተዋል።

ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼኽ ሞሃሙድ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተቀብለዋቸዋል።

“ባለፈው አንድ ዓመት እየሰራንባቸው የቆየነውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ውይይቶች በመቀጠል ፍሬያማ ውይይት አድርገናል” ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባጋሩት መልዕክት።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ “የሃሳብ ልውውጣችን የወል የቅድሚያ ጉዳዮቻችንን ለመከወን ብሎም ለጠንካራ ግንኙነት፣ ቀጠናዊ መረጋጋት እና ልማት ያለንን ቁርጠኝነት በድጋሚ ያፀና ነበር” ማለታቸው ተዘግቧል።