ማሻ ፣ የሀምሌ 07፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) መድረኩን በመክፈቻ ንግግር ያስጀመሩት የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ ወንድሙ ኩርታ ምክር ቤቱ የክልሉን አስፈፃሚ አካላት ተግባር በየደረጃው በመገምገም የተሻለ ውጤት እንዲመዘገብ ሲሰራ መቆየቱን አንስተዋል።
አክለውም የመድረኩን አላማ በማስረዳት፣ የአፈፃፀም ሪፖርቱ የምክር ቤቱን ደንብ በጠበቀ መልኩ እንዲቀርብ አሳስበው መድረኩን በይፋ አስጀምረዋል።
በዚህም መሰረት ህግ፣ ፍትህና መልካም አስተዳደር፣ ግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች፣ በጀትና ፋይናንስ፣ ከተማና መሠረተ ልማት እንዲሁም ማህበራዊ ጉዳይ ዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች በየዘርፉ ውይይት በማድረግ ላይ ይገኛሉ።
መድረኩ ለተከታታይ 2 ቀናት እንደሚካሄድ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
በመድረኩ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ ወንድሙ ኩርታ፣ ምክትል አፈ ጉባኤ ክብርት ወ/ሮ ፀሀይ ደርጫን ጨምሮ ሌሎች የክልሉ አመራሮችና የየዘርፉ ባለሙያዎች እየተሳተፉ እንደሚገኙ የደቡብ ሚዲያ ኔትወርክ ዘግቧል።
ክልል ኮሚኒኬሽን
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።