ማሻ ፣ የሀምሌ 04፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) ኮሚሽኑ በክልሉ 34 ወረዳዎች የአደጋ ስጋት እንዳለባቸው አስታውቋል።
የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ዶክተር ለማ መሰለ በክልሉ ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ አካባቢዎችን በመለየት በርካታ ተግባራት ሲከናወኑ መቆየታቸውን አስታውሰዋል።
በክልሉ 34 ወረዳዎች ውስጥ የሚገኙ 269 ቀበሌዎች የአደጋ ስጋት ቀጠናዎች ተብለው መለየታቸውን አንስተዋል።
ከሰሞኑ በካፋ ዞን ጨና ወረዳ ኮዳ ቀበሌ በደረሰ የመሬት መንሸራተት አደጋ ከ290 በላይ ዜጎች ከመኖሪያቸው መፈናቀላቸውን ተናግረዋል።
ከዝናብ መጨመር ጋር ተያይዞ መሰል ጉዳት እንዳይደርስ ማህበረሰቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግ አሰገንዝበዋል።
ጉዳቶችን ለመቀነስ በኮሚሽኑ የሚሰሩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸው ፤ አደጋው የደረሰበት ጨና ወረዳ ኮዳ ቀበሌ የምግብና የሰብዓዊ ድጋፎችን ተደራሽ ለማድረግ በቂ ዝግጅት መኖሩን አስረድተዋል።
አደጋ የደረሰባቸውን ዜጎች በዘላቂነት ለማቋቋም የሚደረገውን ጥረት በየደረጃው ያሉ አካላት መደገፍ እንዳለባቸው ዶክተር ለማ አሳስበዋል።
አሁን ወቅቱ ዝናብ የሚበረታበት በመሆኑ ፤ ህብረተሰቡ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ መልዕክት አስተላልፈዋል ሲል ደሬቴድ ቦንጋ ቅርንጫፍ ዘግቧል።
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።