June 21, 2025

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

ኢራን በእስራኤል ጥቃት የተገደሉባት የኒውክሌር ሳይንቲስቶች ቁጥር 10 ደረሰ

ማሻ ፣ የሰኔ 14፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) እስራኤል በሀገሪቱ ላይ ባደረሰችው ጥቃት ሌላ የኒውክሌር ሳይንቲስት መሞቱን፤ የኢራን መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።

ይህም በእስራኤል የተገደሉ የኢራን ኒውክሌር ሳይንቲስቶችን ቁጥር 10 አድርሶታል።

ኢሳር ታባታቤይ የተባለው ተመራማሪ ሞት ይፋ የሆነው በቴህራን ሻሪፍ ዩኒቨርሲቲ ጋዜጣ ሲሆን፤ ኢሳር የዩኒቨርሲቲው የቀድሞ ተማሪ ነበር ሲል የዘገበው ቢቢሲ ነው።

ኢራን ቀደም ሲል ሌሎች ዘጠኝ የኒውክሌር ሳይንቲስቶች መሞታቸውን ማረጋገጧ ይታወሳል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ‘ቻናል 12’ የተባለው የእስራኤል ሚዲያ እስራኤል በኢራን በጀመረችው ዘመቻ፤ 9 የኢራን የኑክሌር ሳይንቲስቶችን በአንድ ጊዜ፤ እንዲሁም አሥረኛውን የኒውክሌር ሳይንቲስት በሌላ ጥቃት መግደሏን ዘግቧል።

ኢቢሲ