“የኢራንን ሉዓላዊነት እስከመጨረሻው እስትንፋሳችን እናስጠብቃለን!” – የኢራን ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም
ማሻ ፣ የሰኔ 08፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) “ለሀገራቸው ነብሳቸውን ከማይሰስቱ ጀግና ወታደሮቻችን ጋር በመሆን የኢራንን ሉዓላዊነት እስከመጨረሻው እስትንፋሳችን እናስጠብቃለን” ሲሉ የኢራን ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ሜጀር ጄነራል አሚር ሃታሚ ገለፁ።
የቀድሞ የኢራን ወታደራዊ መኮንን የነበሩት ሜጀር ጄነራል አሚር ለተሰየሙበት ኃላፊነት ዝግጁ መሆናቸውንም ባጋሩት መልዕክት ገልፀዋል።
ከቀናት በፊት በእስራኤል ጥቃት ሕይወታቸው ባለፈው አመራሮች የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘንም ገልፀዋል።
ለጥቃቱ አመርቂ የሆነ የአፀፋ ምላሽ ለመስጠት ለሚወሰዱ እርምጃዎች ቁርጠኛ መሆናቸውንም ነው ጠቅላይ ኢታማዦር ሹሙ የተናገሩት።
አክለውም የጦር ሠራዊቱ የሚጠበቅበትን በሟሟላት የውጊያ አቅሙን ለማጠናከር እንደሚሰራ መጥቀሳቸውን የሀገሪቱ ዜና አገልግሎት ዘግቧል።
4ኛ ቀኑን በያዘው የሁለቱ ሀገራት ግጭት በሁለቱም አካላት በኩል የሰዎች ሕይወት ሲያልፍ የመሰረተ ልማት ውድመቶችም ደርሰዋል።
ኢቢሲ
More Stories
በሕንድ የአውሮፕን መከስከስ አደጋ ሕይወታቸውን ያጡ የአንድ ቤተሰብ አባላት …
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በ12 ሀገራት ላይ የጣሉት የጉዞ እገዳ ተግባራዊ ሆነ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የኢትዮጵያን ታላቁን የክብር ኒሻን ለቢል ጌትስ ሸለሙ