ማሻ ፣ የሰኔ 07፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም)ከመላው ኢትዮጵያ ከተውጣጡ የመምህራን ተወካዮች ጋር ውይይት ያደረጉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፤ የመምህራን ጥያቄዎች ሌሎችንም አካታች በሆነ ማዕቀፍ ሊታዩ የሚችሉ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የመጀመሪያው ሀገር ያለችበትን ነባራዊ ሁኔታ ግምት ውስጥ ያስገባ መሆን እንዳለበት ጠቅሰው፤ ከዚያ ውጭ የሚቀርበው ንጽጽር ግን ኢትዮጵያ ካለችበት ነባራዊ ሁኔታ ጋር ስለማይሄድ ዋጋ የለውም ብለዋል።
ነጻ ሕክምና፣ ነጻ ትምህርት፣ መኖሪያ ቤት የመሳሰሉት ጥያቄዎች ሲጠየቁ የወታደሩን፣ የሐኪሙን እና የሌላውንም ደምሮ ማየት እንደሚያስፈልገ አመላክተዋል።
“እኔ በሕይወት እያለሁ መምህራን መኪና ኖሯቸው፣ መኪናቸውን በሚያስተምሩበት ትምህርት ቤታቸው በር ላይ አቁመው ሲያስተምሩ ከማየት በላይ ለኔ ደስታ የለም” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ውስጥ ውስጡን እየተሠሩ ያሉት ሥራዎች ሲሳኩ የመምህራን ጥያቄዎች ምላሽ ያገኛሉ ብለዋል።
የመምህራን ጥያቄ በደመወዝ ጭማሪ ብቻ የማይመለስ መሆኑን አንስተው፣ የደመወዝ ጭማሪው ላይ ብቻ ትኩረት ከተደረገ ያለችው ተበልታ ታልቃለች በማለት የሚከተለውን መዛባት ጠቁመዋል።
ያለችውን በልቶ ከመጨረስ በራስ ላይ ጨክኖ ገበታን ማስፋት፤ ለዚህ ደግሞ ምርትን ማብዛት አስፈላጊ እንደሆነ ገልጸዋል።
የመምህራን ጥያቄ ከሌሎች ጥያቄዎች ጋር ታይቶ ነገን ታሳቢ ባደረገ መልኩ መመለስ እንደሚቻል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናግረዋል።
ኢቢሲ
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።