ማሻ ፣ የሰኔ 07፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም)ከመላው ኢትዮጵያ ከተውጣጡ የመምህራን ተወካዮች ጋር ውይይት ያደረጉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፤ የመምህራን ጥያቄዎች ሌሎችንም አካታች በሆነ ማዕቀፍ ሊታዩ የሚችሉ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የመጀመሪያው ሀገር ያለችበትን ነባራዊ ሁኔታ ግምት ውስጥ ያስገባ መሆን እንዳለበት ጠቅሰው፤ ከዚያ ውጭ የሚቀርበው ንጽጽር ግን ኢትዮጵያ ካለችበት ነባራዊ ሁኔታ ጋር ስለማይሄድ ዋጋ የለውም ብለዋል።
ነጻ ሕክምና፣ ነጻ ትምህርት፣ መኖሪያ ቤት የመሳሰሉት ጥያቄዎች ሲጠየቁ የወታደሩን፣ የሐኪሙን እና የሌላውንም ደምሮ ማየት እንደሚያስፈልገ አመላክተዋል።
“እኔ በሕይወት እያለሁ መምህራን መኪና ኖሯቸው፣ መኪናቸውን በሚያስተምሩበት ትምህርት ቤታቸው በር ላይ አቁመው ሲያስተምሩ ከማየት በላይ ለኔ ደስታ የለም” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ውስጥ ውስጡን እየተሠሩ ያሉት ሥራዎች ሲሳኩ የመምህራን ጥያቄዎች ምላሽ ያገኛሉ ብለዋል።
የመምህራን ጥያቄ በደመወዝ ጭማሪ ብቻ የማይመለስ መሆኑን አንስተው፣ የደመወዝ ጭማሪው ላይ ብቻ ትኩረት ከተደረገ ያለችው ተበልታ ታልቃለች በማለት የሚከተለውን መዛባት ጠቁመዋል።
ያለችውን በልቶ ከመጨረስ በራስ ላይ ጨክኖ ገበታን ማስፋት፤ ለዚህ ደግሞ ምርትን ማብዛት አስፈላጊ እንደሆነ ገልጸዋል።
የመምህራን ጥያቄ ከሌሎች ጥያቄዎች ጋር ታይቶ ነገን ታሳቢ ባደረገ መልኩ መመለስ እንደሚቻል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናግረዋል።
ኢቢሲ
More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።
የሰው ተኮር ተግባራት በማጠናከር ሁለተናዊ ዕድገትን ለማረጋገጥ የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበበ ማሞ ገለፁ።