ማሻ ፣ የግንቦት 15፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) ‹‹ትውልድ በመምህራን ይቀረፃል፣ ሀገር በትምህርት ይበለጽጋል” በሚል መሪ ቃል ከሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ካምፓስ መምህራን ጋር የውይይት መድረክ ተካሂዷል ።
በዚህ መድረክ ላይ የተገኙት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ደን አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ቁጥጥር ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ኢንጂነር አስራት ገብረማርያም በመክፈቻ ንግግራቸው እንደገለፁት የከፍተኛ ትምህርት ተቋመት ትውልዱ በጥሩ ስነ ምግባርና በእውቀት ታንፀው ለሀገር መንግሥት ግንባታ ህደት ውስጥ የድርሻቸውን እንድወጡ ከማድረግ አንፃር ትልቅ ሚና እንዳላቸው ገልፀዋል ።
ከለውጡ ወድህ የተለያዩ ችግሮችን በማለፍ በብልፅግና እሳቤ ዘርፈ ብዙ ድሎች እየተመዘገቡ ይገኛል ያሉት የቢሮ ኃላፊዎች የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትም ድሎችን ለማስቀጠል በምደረገው ጥረት ውስጥ የድርሻቸውን እንድወጡ ነው የተናገሩት ።
በመድረኩ የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የቴፒ ካምፓስ ስራ አስፈፃሚ አቶ መንግስቱ ከተማ ‹‹ትውልድ በመምህራን ይቀረፃል፣ ሀገር በትምህርት ይበለጽጋል የሚል የመወያያ ሰነድ ባቀረቡበት ወቅት በመማር ማስተማር ህደት ያሉትን ችግሮች ለይቶ የመፍትሔ አቅጣጫዎችን ከማስቀመጥ አኳያ ትኩረት ልደረግ እንደምገባ ገልፀዋል ።
በመድረኩ የክልሉ ደን፣ አካባቢ ጥበቃና አየር ንብረት ለዉጥ ቁጥጥር ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ኢንጅነር አስራት ገብረማርያም ፣የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ካምፓስ ስራ አስፈፃሚ አቶ መንግስቱ ከተማን ጨምሮ የዩኒቨርሲቲው የስራ ኃላፊዎችና መምህራኖች ተሳትፈዋል።
ዘጋቢ አስቻለው አየለ
More Stories
በሀገሪቱ የኢኮኖሚ ግንባታ ሂደት የነጋዴዉ ማህበረሰብ ሚና ጉልህ መሆኑን የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበበ ማሞ ገለጹ።
በዘንድሮ ዓመት በሚሰጠዉ የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና አጠቃላይ ከሚፈተኑ 19ሺህ በላይ ተማሪዎች ዉስጥ ከ2ሺህ 6መቶ በላይ ተማሪዎች በኦንላይን ፈተና እንደሚፈተኑ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ትምህርት ቢሮ አስታወቀ ።
ከውሃ ሀብት የሚገኘውን ጥቅም ለማጎልበት መስራት ያስፈልጋል – ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር ኢ/ር)