ማሻ ፣ የግንቦት 15፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) የብልጽግና ጉዞና የነጋዴዉ ማህበረሰብ ሚና በሚል መሪ ቃል በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ ዞን አቀፍ ምክክር ከንግዱ ማህበረሰብ ጋር ተካሂዷል።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበበ ማሞ በሀገሪቱ የኢኮኖሚ ግንባታ ህደት ዉስጥ የነጋዴዉ ማህበረሰብ ሚና ጉልህ መሆኑን ገልጸዋል።
አያይዘዉ ለማንኛዉ ልማት መረጋገጥና ዘላቂ ሰላም አይተከ ሚና ስላለዉ አሁን በዞኑ ያለዉን ሰላም በዘላቂነት ለማስጠበቅ ነጋዴዉ ማህበረሰብ የድርሻዉን አንዲወጣ አሰሳስበዋል።
በመድረኩም በሀገሪቱ ለዉጡን ተከትሎ በሀገር አቀፍ ደረጃ እስካሁን በተመዘገቡ ስኬቶችና ባጋጠሙ ተግዳሮቶች እንዲሁም በቀጣይ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሆኑ ነጋዴዎችን ለመፍጠር የሚያስችሉና መሰል ጉዳዮች ላይ በሸካ ዞን ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ ተግባሩ አንደሻ የዉይይት መነሻ ሰነድ እየቀረበ ሲሆን ነጋዴዎቹም መክረዉ የጋራ አቅጣጫ እንደሚያስቀሚጡ ይጠበቃል።
ዘጋቢ ጌትነት ገረመዉ
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።