ማሻ ፣ የግንቦት 15፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) የብልጽግና ጉዞና የነጋዴዉ ማህበረሰብ ሚና በሚል መሪ ቃል በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ ዞን አቀፍ ምክክር ከንግዱ ማህበረሰብ ጋር ተካሂዷል።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበበ ማሞ በሀገሪቱ የኢኮኖሚ ግንባታ ህደት ዉስጥ የነጋዴዉ ማህበረሰብ ሚና ጉልህ መሆኑን ገልጸዋል።
አያይዘዉ ለማንኛዉ ልማት መረጋገጥና ዘላቂ ሰላም አይተከ ሚና ስላለዉ አሁን በዞኑ ያለዉን ሰላም በዘላቂነት ለማስጠበቅ ነጋዴዉ ማህበረሰብ የድርሻዉን አንዲወጣ አሰሳስበዋል።
በመድረኩም በሀገሪቱ ለዉጡን ተከትሎ በሀገር አቀፍ ደረጃ እስካሁን በተመዘገቡ ስኬቶችና ባጋጠሙ ተግዳሮቶች እንዲሁም በቀጣይ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሆኑ ነጋዴዎችን ለመፍጠር የሚያስችሉና መሰል ጉዳዮች ላይ በሸካ ዞን ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ ተግባሩ አንደሻ የዉይይት መነሻ ሰነድ እየቀረበ ሲሆን ነጋዴዎቹም መክረዉ የጋራ አቅጣጫ እንደሚያስቀሚጡ ይጠበቃል።
ዘጋቢ ጌትነት ገረመዉ
More Stories
በጥናት ምርምር የተደገፍ ማህበረሰብ ተኮር ተግባራትን ከመፈፀም ባሻገር በጥሩ ስነ ምግባርና እወቀት የታነፁ ትውልድን ከመቅረፅ አኳያ የዩንቨርስቲ መምህራኖች ሚና የጎላ እንደሆነ ተገለፀ።
በዘንድሮ ዓመት በሚሰጠዉ የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና አጠቃላይ ከሚፈተኑ 19ሺህ በላይ ተማሪዎች ዉስጥ ከ2ሺህ 6መቶ በላይ ተማሪዎች በኦንላይን ፈተና እንደሚፈተኑ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ትምህርት ቢሮ አስታወቀ ።
ከውሃ ሀብት የሚገኘውን ጥቅም ለማጎልበት መስራት ያስፈልጋል – ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር ኢ/ር)