ማሻ ፣ የግንቦት 08፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) በሸካ ዞን ማሻ ወረዳ የ2017 ዓ/ም የበልግ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር በማሻ ወረዳ ጋዳ ቀበሌ የማብሰሪያ ፕሮግራም ተካሄዷል ።
በማስጀመሪያ ፕሮግራም ላይ የተገኙት የማሻ ወረዳ ምክትል ዋና አስተዳዳሪና የመንገድና ትራንስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተግባሩ እዳሮ እንዳሉት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ጥምር ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች ይተከላሉ ብለው እንክብካቤም በአግባቡ መደረግ እንዳለበት አንስተዋል።
የማሻ ወረዳ ግብርና ደን አከባቢ ጥበቃ ህብረት ስራ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ልሳኑ አለማየሁ በበኩላቸው በወረዳው በ2017 የበልግ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር 3 መቶ 63 ሺህ 1መቶ 90 ለመትከል ዕቅድ መያዙን ገልፀው በጠቅላላ በ2017 ዓ/ም 3 ሚሊዮን 7መቶ 14 ሺህ 880 ችግኝ ለመትከል መታቀዱን ተናግረዋል ።
የተለያዩ ጠቀመታ ያላቸው 3 ሚሊዮን 922ሺህ ችግኝ መዘጋጀቱንም ገልፀዋል።
በመርሃ ግብሩ የወረዳው ምክትል ዋና አስተዳደርና የመንገድና ትራንስፖርት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ተግባሩ እዳሮ፤ የወረዳዉ የጽ/ቤት ሀላፊዎች፤ ባለሙያዎችና የአከባቢ ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
በልጃለም ማሞ
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።