ማሻ ፣ የግንቦት 08፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) በሸካ ዞን ማሻ ወረዳ የ2017 ዓ/ም የበልግ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር በማሻ ወረዳ ጋዳ ቀበሌ የማብሰሪያ ፕሮግራም ተካሄዷል ።
በማስጀመሪያ ፕሮግራም ላይ የተገኙት የማሻ ወረዳ ምክትል ዋና አስተዳዳሪና የመንገድና ትራንስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተግባሩ እዳሮ እንዳሉት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ጥምር ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች ይተከላሉ ብለው እንክብካቤም በአግባቡ መደረግ እንዳለበት አንስተዋል።
የማሻ ወረዳ ግብርና ደን አከባቢ ጥበቃ ህብረት ስራ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ልሳኑ አለማየሁ በበኩላቸው በወረዳው በ2017 የበልግ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር 3 መቶ 63 ሺህ 1መቶ 90 ለመትከል ዕቅድ መያዙን ገልፀው በጠቅላላ በ2017 ዓ/ም 3 ሚሊዮን 7መቶ 14 ሺህ 880 ችግኝ ለመትከል መታቀዱን ተናግረዋል ።
የተለያዩ ጠቀመታ ያላቸው 3 ሚሊዮን 922ሺህ ችግኝ መዘጋጀቱንም ገልፀዋል።
በመርሃ ግብሩ የወረዳው ምክትል ዋና አስተዳደርና የመንገድና ትራንስፖርት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ተግባሩ እዳሮ፤ የወረዳዉ የጽ/ቤት ሀላፊዎች፤ ባለሙያዎችና የአከባቢ ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
በልጃለም ማሞ
More Stories
የኢትዮጵያ መንግሥት የ3.5 ቢሊዮን ዶላር የዕዳ ሽግሽግ ለማድረግ የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ከአበዳሪዎች ኮሚቴ ጋር ተፈራረመ
በግብርናው ዘርፍ ኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነቷን ማረጋገጥ አለባት የሚል ግብ ተይዞ እየተሰራ ነው፡- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
የ2018 የፌዴራል መንግሥት በጀት 1 ነጥብ 93 ትሪሊየን ብር ሆኖ ጸደቀ