ማሻ ፣ የግንቦት 03፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) የዩክሬን ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዜሌንስኪ ሩስያ ለቀጥታ የሰላም ንግግሮች ያቀረበችውን ሀሳብ በደስታ በመቀበል ነገር ግን ድርድር ከመጀመሩ በፊት የተኩስ አቁም መኖር እንዳለበት አጥብቀው አሳስበዋል።
ዘሌንስኪ በኤክስ ገፃቸው ላይ፥ የሩስያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን የቀጥታ ውይይት ለመጀመር ያቀረቡትን ጥሪ “በጎ ምልክት” በማለት ገልፀውታል።
አያይዘውም፥ “መላው ዓለም ይህን ለረጅም ጊዜ ሲጠብቀው ቆይቷል” ብለዋል።
ሆኖም ግን ማንኛውንም ግጭት ለማስቆም የመጀመሪያው እርምጃ መሆን ያለበት የተኩስ አቁም ስምምነት ነው ብለዋል።
ኢቢሲ
More Stories
ትራምፕ ቲክ ቶክን የሚገዙ የአሜሪካ ባለሀብቶች ማግኘታቸውን ገለፁ
ሩሲያ እና ህንድ በጦር መሳሪያ አቅርቦት ላይ ያላቸውን ትብብር ለማሳደግ እንደሚሰሩ አስታወቁ፡፡
ኢራን በእስራኤል ጥቃት የተገደሉባት የኒውክሌር ሳይንቲስቶች ቁጥር 10 ደረሰ