ማሻ ፣ የመጋቢት 29፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) 272 ሚሊየን ብር ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች መያዙን የጉምሩክ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡
ኮሚሽኑ ከመጋቢት 18 እስከ 25 ቀን 2017 ዓ.ም ባደረገው ክትትል ነው 187 ነጥብ 4 ሚሊየን ብር የገቢ እና 84 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር የወጪ የኮንትሮባንድ እቃዎች የያዘው፡፡
ከተያዙት የኮንትሮባንድ እቃዎች መካከል ማዕድናት፣ አልባሳት፣ ቡና፣ የተሽከርካሪ መለዋወጫ፣ አደንዛዥ እጾች፣ መድሃኒትና የውጭ ሀገራት ገንዘቦች እንደሚገኙ ተገልጿል፡፡
የኮንትሮባንድ እቃዎቹን ሲያዘዋውሩ ነበር የተባሉ 8 ተጠርጣሪዎች እና 7 ተሽከርካሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውንም የኮሚሽኑ መረጃ ያመላክታል፡፡
ፋና
More Stories
ብልጽግና በሃሳብ የበላይነት የሚያምን ፓርቲ ነው ፦ አቶ ሰብስቤ ሻዎኖ
በቀጣዮቹ ቀናት በበርካታ አካባቢዎች የክረምቱ ዝናብ ተጠናክሮ ይቀጥላል
በአዕምሮ የበለጸገ ትውልድ እንዲፈጠር የምግብ -ስርዓትና ስርዓተ – ምግብ ትግበራዎችን በቅንጅት መምራት እንደሚገባ ተገለጸ