ማሻ ፣ የመጋቢት 29፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) 272 ሚሊየን ብር ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች መያዙን የጉምሩክ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡
ኮሚሽኑ ከመጋቢት 18 እስከ 25 ቀን 2017 ዓ.ም ባደረገው ክትትል ነው 187 ነጥብ 4 ሚሊየን ብር የገቢ እና 84 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር የወጪ የኮንትሮባንድ እቃዎች የያዘው፡፡
ከተያዙት የኮንትሮባንድ እቃዎች መካከል ማዕድናት፣ አልባሳት፣ ቡና፣ የተሽከርካሪ መለዋወጫ፣ አደንዛዥ እጾች፣ መድሃኒትና የውጭ ሀገራት ገንዘቦች እንደሚገኙ ተገልጿል፡፡
የኮንትሮባንድ እቃዎቹን ሲያዘዋውሩ ነበር የተባሉ 8 ተጠርጣሪዎች እና 7 ተሽከርካሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውንም የኮሚሽኑ መረጃ ያመላክታል፡፡
ፋና
More Stories
የደቡብ ሬድዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የማሻ ቅርንጫፍ ጣቢያ በመምህር ዳኪቶ ጋወቶ ድንገተኛ ህልፈት የተሰማዉን ጥልቅ ሀዘን ገለፀ።
ማንቼስተር ዩናይትድ አርሰናልን በገዛ ሜዳው አሸነፈ
መልካም አብነቶች በማስፋት ወደ ብልጽግና የሚደረገውን ጉዞ እናፋጥናለን – ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)