ማሻ ፣ የመጋቢት 24፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) ይህን የገለፁት የሸካ ዞን ልዩ የአዳሪ ትምህርት ማስጀመሪያ መረሃ ግብር ሁሉም ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በቴፒ ከተማ በተካሄደበት ወቅት ነው።
የመመዘኛ ፈተና አልፈው በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ልዩ አዳር ትምህርት ለመማር ከመጡት ተማሪዎች መካከል አንዳንዶቹ እንደገለፁት ይህ አድል መፈጠሩ የተሻለ ውጤት በማስመዝገብ ተወዳዳሪ እንድሆኑ እንደሚያግዛቸው ነው ።
ትኩረታችን በተሻለ እውቀት ወደ ተሻለ ደረጃ መድረስ ነው ያሉት ተማሪዎቹ አሁንሥ በየደረጃው የሚገኙ ባለድርሻ አካላት ድጋፍና ክትትል ስራዎችን እንድያጠናክሩ ጠይቀዋል ።
የተማሪ ወላጆችም በበኩላቸው የዞን መንግሥትና በየደረጃው የሚገኙ አካላት ይህን እድል በማመቻቸቱ አመስግነው ልጆቻቸውን በተለየ መልኩ ክትትል እንደሚያደርጉ ገልጸዋል ።
ብቁና ተወዳዳሪ የሆኑ ተማሪዎችን ለማፍራት የአዳሪ ትምህርት ቤቶችን ማስፋፋት እንደሚያስፈልግ ተናግረው የዘርፉን ስራ ለመደገፍ የበኩላቸውን እንደሚወጡ ጠቁመዋል ።
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።