መጋቢት 24፣ 2017 ግንባታው ሊጠናቀቅ ለተቃረበው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ ቀረበ፡፡
ታላቁ የሕዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት፤ ለኢትዮጵያውያን፣ ትውልደ ኢትዮጵያውያን እና ለኢትዮጵያ ወዳጆች የግድቡ ግንባታ መሠረተ-ድንጋይ ለተቀመጠበት 14ኛ ዓመት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፏል፡፡
በመልዕክቱም፤ የግድቡ ግንባታ ለፍጻሜ መቃረቡን በማኅበራዊ ትሥሥር ገጹ አስታውቋል፡፡
ግድቡ በመላው ሕዝብ ሁለንተናዊ ድጋፍ እየተከናወነ መሆኑ፣ ግንባታውም አንድነትን ማጠናከሩ፣ በደማቅ የዲፕሎማሲ ድል ታጅቦና የኢትዮጵያን ገፅታ በመገንባት ዘንድሮ 14ኛ ዓመቱን መያዙም ተጠቅሷል፡፡
ለዚህ ድል የበቃነው በኅብረት ችለን በመቆማችን ነው ያለው ጽሕፈት ቤቱ፤ ለሌሎችም ሀገራዊ ጉዳዮች የበለጠ በጋራ መቆም እንዳለብን ለእኛም ትምህርት ለዓለምም ምሳሌ ነው ብሏል፡፡
የሚደረገው ሁሉን አቀፍ ድጋፍም ግንባታው እስከሚጠናቀቅ ድረስ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርቧል፡፡
(ኤፍ ኤም ሲ)
More Stories
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።
የሰው ተኮር ተግባራት በማጠናከር ሁለተናዊ ዕድገትን ለማረጋገጥ የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበበ ማሞ ገለፁ።
የህዳሴው ግድብ መጠናቀቅ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ትስስርን ያሳድጋል