ለይፋዊ የስራ ጉብኝት በኢትዮጵያ የሚገኙት የእንግሊዟ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አንጄላ ሬይነር በሀገሪቱ መንግሥት የተራድኦ ድርጅት የተገዙ 12 አምቡላንሶችን ለኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር አስረክበዋል።
አምቡላንሶቹን የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ፕሬዚዳንት አበራ ቶላ ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሯ ተረክበዋል።
አምቡላንሶቹ ለእናቶችና ህፃናት አስቸኳይ ሰብዓዊ አገልግሎት የሚውሉ የህክምና ግብዓቶችን ያሟሉ መሆናቸውም ተመላክቷል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አንጄላ ሬይነር የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ሰብዓዊ ተግባራትን የጎበኙ ሲሆን ከማኅበሩ አመራሮች በትብብር በሚሰሯቸው ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል።
More Stories
የክልሉ ጤና ባለሙያዎችና የጤና ተቋማት አመራሮች ያሳዩት አቋም ለህዝባቸው ያላቸውን ውግንና እና ለሙያቸው ያላቸውን ክብር ያረጋገጡበት ነው :- የክልሉ ርዕስ መስተዳድር ዶክተር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ ገለፁ ።
በክልሉ ሁሉም ቀበሌዎች የተቀናጀ 2ኛ ዙር የልጅነት ልምሻ በሽታ መከላከያ ክትባት ከግንቦት 22-25/2017 ዓ.ም እንደሚሰጥ ተገለጸ።
ከጤና ሚኒስቴር እና ከኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት MPox አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ