ማሻ፡ ጥር 04/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ ማሻ ቅርንጫፍ) በሚዛን አማን ከተማ ለቢስት ባር እሮጣለሁ በሚል መሪ ቃል የ5 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ተካሂዷል።
የቤንች ብሄር ዘመን መለወጫና የምስጋና በዓል “ቢስት ባር” በነገው ዕለት በድምቀት የሚከበር ሲሆን በዓሉን ምክንያት በማድረግ የጎዳና ላይ ሩጫ ተደርጓል።
በሩጫው ላይ የዞኑ አመራሮችን ጨምሮ በርካታ የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል።
በውድድሩ ላሸነፉ ተሳታፊዎች የምስክር ወረቀትና የገንዘብ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
More Stories
የ2026 የካራባኦ ዋንጫ ፍፃሜ …
ሴኔጋል የአፍሪካ ዋንጫ ሻምፒዮንነቷ እንዲሰረዝ መወሰኑ አሳፋሪ ነው፡- የካፍ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ኦጉስቲን ሴንግሆር
ቦርንማውዝ ከ ማንችስተር ዩናይትድ