ሰደድ እሳቱን ለመቆጣጠር የሚደረገውን ጥረት እያስተጓጎለ ያለው ከፍተኛ ነፋስም እሳቱ እንዲዛመትና እንዲስፋፋ እያደረገ መሆኑ ተገልጿል፡፡
በዚህም ሰደድ እሳቱ ከሆሊውድ መንደሯ ሎስ አንጀለስ አልፎ ወደ ሌሎች አካባቢዎች የመዛመት ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑ እየተነገረ ነው፡፡
እሳቱን ለማጥፋት በሚደረገው ርብርብም ከመደበኛ የአደጋ ጊዜ ሠራተኞች በተጨማሪ 1 ሺህ የሚጠጉ የሕግ ታራሚዎች እየተሳተፉ መሆኑን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
ታራሚዎቹ እያደረጉት ላለው አስተዋጽኦ ክፍያ እንደሚፈጸምላቸው እና ይህም በካሊፎርኒያ የእርምት እና የመልሶ ማቋቋም መምሪያ (ሲሲአር) የሚመራ የረዥም ጊዜ የበጎ ፈቃድ መርሐ-ግብር አካል መሆኑን ዘገባው አመላክቷል፡፡
እስከ አሁን ከ10 ሺህ በላይ ሕንጻዎችን ያወደመው ሰደድ እሳቱ÷ በ37 ሺህ ሔክታር ላይም ጉዳት ማድረሱ ተገልጿል፡፡
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የአውሮፓ ህብረት ያወጣቸውን ደንቦች መሠረት በማድረግ የግብርና ምርቶች ከደን ጭፍጨፋ ነፃ ሆነው እንዲመረቱ ከማድረግ አንፃር የግብርና ባለሙያዎች ሚና የጎላ እንደሆነ ተገለፀ ።