ሰደድ እሳቱን ለመቆጣጠር የሚደረገውን ጥረት እያስተጓጎለ ያለው ከፍተኛ ነፋስም እሳቱ እንዲዛመትና እንዲስፋፋ እያደረገ መሆኑ ተገልጿል፡፡
በዚህም ሰደድ እሳቱ ከሆሊውድ መንደሯ ሎስ አንጀለስ አልፎ ወደ ሌሎች አካባቢዎች የመዛመት ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑ እየተነገረ ነው፡፡
እሳቱን ለማጥፋት በሚደረገው ርብርብም ከመደበኛ የአደጋ ጊዜ ሠራተኞች በተጨማሪ 1 ሺህ የሚጠጉ የሕግ ታራሚዎች እየተሳተፉ መሆኑን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
ታራሚዎቹ እያደረጉት ላለው አስተዋጽኦ ክፍያ እንደሚፈጸምላቸው እና ይህም በካሊፎርኒያ የእርምት እና የመልሶ ማቋቋም መምሪያ (ሲሲአር) የሚመራ የረዥም ጊዜ የበጎ ፈቃድ መርሐ-ግብር አካል መሆኑን ዘገባው አመላክቷል፡፡
እስከ አሁን ከ10 ሺህ በላይ ሕንጻዎችን ያወደመው ሰደድ እሳቱ÷ በ37 ሺህ ሔክታር ላይም ጉዳት ማድረሱ ተገልጿል፡፡
More Stories
እንግሊዝን ያስቆጣው የኢራን ጥቃት
በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ በሌማት ትሩፋት መርሐግብር የተሠማሩ ወጣቶች ተጠቃሚ እየሆኑ መምጣቸው ተገለጸ።
ኢራን ላይ እየተካሄደ የሚገኘው ወታደራዊ ዘመቻ …