በሶስት አህጉራት የሚገኙት አዲስ አባል ሀገራቱ ቤላሩስ፣ ቦልቪያ፣ ኢንዶኖዥያ፣ ካዛኪስታን፣ ኩባ፣ ማሌዥያ፣ ታይላንድ፣ ኡጋንዳ እና ኡዝቤከስታን መሆናቸው ታውቋል፡፡
የአዲስ አባል ሀገራቱ የአባልነት ጥያቄ ቀደም ሲል በሩሲያ ካዛን በተካሄደው 16ኛው የብሪክስ የመሪዎች ጉባኤ ላይ መፅደቁ ነው የተገለፀው፡፡
የብሪክስ አባል ለመሆን ከ30 በላይ ሀገራት ጥያቄ አቅርበው እንደነበር የተገለፀ ሲሆን አዲሶቹ ዘጠኝ አባል ሀገራቱ በብሪክስ መሪዎች ተገምገመው የአባልነት ጥያቄቸው ተቀባይነት ማግኘቱ ተመላክቷል፡፡
በቅርቡም ተጨማሪ አራት ሀገራት ብሪክስን ይቀላቀላሉ ተብሏል፡፡
በብራዚል፣ ሩሲያ፣ ህንድ፣ ቻይና እና ደቡብ አፍሪካ የተመሰረተው የብሪክስ የኢኮኖሚ ቡድን በፈረንጆቹ 2024 ኢትዮጵያን ጨምሮ አራት ሀገራትን በአባልነት መቀበሉ ይታወሳል።
አዳዲስ አባል ሀገራት መቀላቀላቸውን ተከትሎም 9 አባላት የነበሩት ብሪክስ የኢኮኖሚ ቡድን የአባላቱን ቁጥር ወደ 18 ከፍ ማድረጉን ኢራን ፕሬስ እና አር ቲ ዘግበዋል፡፡
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።