በተመሳሳይ ቡና አምራች አርሶ አደር የወይዘሮ ምርትነሽ ታደለ በገማድሮ ቀበሌ የቡና ልማት እንቅስቃሴንም ጎብኝተዋል።
በ2010 ዓ.ም በመንግስት ድጋፍ የቡና ልማት ስራን የጀመሩ መሆናቸውን የተናገሩት ወይዘሮ ምርትነሽ ከዚህ ቀደም የእጅ ማሽን በመጠቀም እያመረቱ ውጤታማ በመሆናቸው የቡና ኢንዱስትሪ ማሽን መትከል መቻላቸውን ተናግረዋል።
በ2016/17 ዓ.ም ምርት ዘመን 1መቶ 50ሺህ ኪ.ግ የታጠበ ቡና እያመረቱ ሲሆን ምርታቸውን ለመሸጥ የገበያ ትስስር ያለመኖርና መንገድ ተግዳሮት እንደሆነባቸው ገልፀዋል።
የበለጠ ውጤታማ ለመሆን የቡና ልማታቸውን የማስፋት ዕቅድ እንዳላቸው ተናግረው መንግስት የብድር አገልግሎት የሚያገኙበትን አቅጣጫ እንዲያመቻች ጠይቀዋል።
በመጨረሻም ስመለከቱ የነበረውን የተለያዩ የልማት ምርቶች ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን ግብረመልስ በመስጠት ለሁለት ቀን ስካሄድ የነበረው የልማት ጉብኝት ተጠናቋል።
በጉብኝቱም የኢፌዲሪ መንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶክተር ለገሰ ቱሉን ጨምሮ የዞን፣የከተማና የወረዳ ከፍተኛ አመራሮች ተሳትፈዋል።
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።