የ19ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ክብረ በዓል አካል የሆነው የዋዜማው የእራት መርሐ-ግብር በጋሞ ምርምር እና ባህል ማዕከል አዳራሽ እየተካሄደ ነው።በመርሐ-ግብሩ ግብሩ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ለገሰ ጫፎ፣ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ቴዎድሮስ ምሕረት፣ የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት እና የዋና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አደም ፋራህ፣ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር)፣ የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች፣ የሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች ከንቲባዎች እንዲሁም የ76ቱ ብሔር፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ተወካዮችን ጨምሮ ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።በመርሐ-ግብሩ ለበዓሉ በድምቀት መዘጋጀት የላቀ አፈፃፀም ላላቸው ክልሎች እና አመራሮች በፌዴሬሽን ምክር ቤት እና በአዘጋጁ ክልል አማካኝነት የምስጋና እና የእውቅና ሽልማት ይሰጣል።
EBC
More Stories
መንግስት በፈጠራና ክህሎት ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው – ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
ሀገራዊ የጤና ፖሊሲ ከመከላከልባሻገር አክሞ መዳንን መሰረት ያደረገ ስራን መስራት እንደሚገባ ተገለፀ።
በኢራን ወደብ በደረሰ ፍንዳታ 25 ሰዎች ህይወታቸው አለፈ