ሶማሊያ ውስጥ አልሸባብን እየተዋጉ ያሉ በሺዎች የሚቆጠሩ ወታደሮች ያላት ወደብ አልባዋ ኢትዮጵያ ባለፈው የፈረንጆቹ አዲስ አመት ከራስ ገዟ ሶማሊላንድ ጋር ወደብ ለመገንባት የተፈራረመችው ስምምነት ሞቃዲሹን አስቆጥቷል።ሶማሊላንድ ለኢትዮጵያ 20 ኪሎሜትር የሚረዝም የባህር ጠረፍ በ50 አመት የሊዝ ኪራይ ለመስጠት የተስማማችው፣ ኢትዮጵያ በምላሹ የሀገርነት እውቅና እንድትሰጣት በመፈለግ ነበር።ሶማሊላንድ በምርጫ ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር የምታደርግ እና ነጻነቷን ካወጀችበት ከ1991 ጀምሮ በአንጻራዊነት ሰላማዊ እና የተረጋጋች ብትሆንም አለምአቀፋዊ የሀገርነት እውቅና ማግኘት አልቻለችም::
al-ain
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።