የሸካቾ ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ “ማሽቃሬ ባሮ” በክልሉ ከሚገኙ ቱባ ባህሎች አንዱ መሆኑንና የህዝቦችን ትስስር ፣አንድነት፣ ህብረብሔራዊነትን በማጎልበት ረገድ ባህል ትልቅ ፋይዳ እንዳለው የክልሉ ባህል ቱርዝም ቢሮ ኃላፊ አቶ ፋንታሁን ተናገሩ ።ባህልን ማልማት፣መንከባከብ ፣መጠበቅ፣ የህዝቦች ትልቅ የማዕዘን ድንጋይ፣መነሻ ታሪካቸውን የሚያዩበት መነጽር፣ ዘላቂ ልማትና ሰላምን ለማረጋገጥ የሚያስችል ወሳኝ እሴት ነው ሲሉም የቢሮው ኃላፍ አክለዋል።የባህልና የቋንቋ መብቶች ተጠብቀው የሚካሄዱት ክዋኔዎች ባህላዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጥቅሙ ከፍተኛ ስለሆነ ለትውልድ ማስተማርና ማስተላለፍ ያስፈልጋል ተብሏል።
የሸካቾ ዘመን መለወጫ/ማሽቃሮ/ በዓል በደማቅ ባህላዊና ታሪካዊ ስነስርዓቶች “በሸካ ዞን አንድራቻ ወረዳ ገጫ” በድምቀት ተከብሮ ውሏል።
More Stories
እንግሊዝን ያስቆጣው የኢራን ጥቃት
በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ በሌማት ትሩፋት መርሐግብር የተሠማሩ ወጣቶች ተጠቃሚ እየሆኑ መምጣቸው ተገለጸ።
ኢራን ላይ እየተካሄደ የሚገኘው ወታደራዊ ዘመቻ …